‹‹የታዳሽ ሀይል ትራንስፓርት በኢትዮጵያ›› በሚል ርዕስ የምክክር መድረክ ተካሄደ
የትራንስፖርት ሚኒስቴር የታዳሽ ሀይል ትራንስፓርት በኢትዮጵያ በሚል ርዕስ ከባለድርሻ አካላት ጋር ያዘጋጀው የምክክር መድረክ ተካሄደ፡፡
የትራንስፖርት ሚንስትር ክብርት ወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስ በምክክር መድረኩ ላይ ባደረጉት ንግግር እንደገለጹት የትራንስፖርት አገልግሎቱን ከብክለት የፀዳ እና ለአካባቢ ተስማሚ እንዲሆን ለማድረግ፣ የግል ዘርፉን ማሳተፍ ጊዜ የሚሰጠው ጉዳይ አለመሆኑን ጠቅሰው የአውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪውን በማዘመን በኤሌክትሪክ እንዲሁም በነዳጅና በኤሌክትሪክ ኃይል የሚሰሩ ተሸከርካሪዎች ወደ ሀገር ውስጥ እንዲገቡና ሀገር ውስጥ እንዲመረቱ ለማድረግ የባለድርሻ አካላቱ ሚና የላቀ መሆኑን ግልጸዋል፡፡
አቶ ምትኩ አስማረ የፌዴራል ትራንስፖርት ባለስልጣን ምክትል ዳይሬክተር ‹‹የታዳሽ ኃይል ትራንስፖርት በኢትዮጲያ›› በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ፁኁፍ ሲያቀርቡ እንደገለጹት የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎችን ጥቅም ላይ ማዋል ዋና አላማ ከብክለት የጸዳ፤ ቀጣይነት ያለው ተደራሽ የሆነ ትራንስፖርት ማቅረብን አለማ እንዳደረገ በገለጻቸው አስቀምጠዋል፡፡
የማራቶን ሞተርስ ኢንጂነሪንግ መስራች ባለቤትና ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መልካሙ አሰፋ እና የቶም ኢ-ባይክ ባለቤትና ስራ አስኪያጅ አቶ ቶማስ ሃይሉ ያላቸውን ልምድና ተሞክሮ ያቀረቡ ሲሆን የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ምንም ዓይነት የበካይ ጋዝ ወይም የካርቦንዳይ ኦክሳይድ ልቀትና የድምጽ ብክለት የማያስከትል መሆኑን ገልጸው ከተሻሻለው የኤክሳይስ ታክስ ጋር በተያያዘ መንግስት የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ጥቅም ላይ እንዲውል እያደረገ ያለውን የማበረታት ስራ አድንቀዋል፡፡
በምክክር መድረኩ ላይ የተሳተፉ ባለድርሻ አካላት በቀጣይ የተሻለ የትራንስፖርት አማራጮችን ለህብረተሰቡ ለማቅረብ ከመንግስት በጋራ እንደሚሰሩ ገልጸዋል፡፡
የዜና ክምችት
-
ጥቅምት 1 ቀን 2013 ዓ.ም ከጠዋቱ 12፡00 ጀምሮ የብስክሌት እና የእግረኞች ቀን መርሃ ግብር በየአካባቢው የእግር ጉዞዎች እና የብስክሌት እንቅስቃሴዎችን በማካሄድ የሞተር አልባ ትራንስፖርት የማበረታታት ፕሮግራም ይካሄዳል፡፡
-
‹‹የታዳሽ ሀይል ትራንስፓርት በኢትዮጵያ›› በሚል ርዕስ የምክክር መድረክ ተካሄደ
-
የተጀመረው ሀገር አቀፍ የመንገድ ትራፊክ ደህንነት ንቅናቄ ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡
-
በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር “ከጳጉሜን እስከ ጳጉሜን #እንደርሳለን!” የመንገድ ትራፊክ ደህንነት ንቅናቄ ጳጉሜን 3 #የቁጥጥር ቀን ሆኖ ተከብሮ መዋሉ ተገለፀ።
-
መስማት የተሳናቸው የህብረተሰብ ክፍሎች የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ተጠቃሚ ለማድረግ የአሰራር ማንዋል ተዘጋጀ
-
የትራንስፖርት ሚኒስቴር የአገልግሎት አሰጣጥ ማሻሻያ የአፈጻጸም ሪፖርት ላይ ዉይይት ተደረገ፡፡
-
‹‹የኮቪድ-19 ወረርሽኝና የሎጂስትክስ ዘርፍ›› በሚል ርዕስ 14 ኛው ዙር ዌብናር ተካሄደ
-
በሶማሌ ክልል ደወሌ ላይ የኮቪድ-19 ስርጭትን ለመከላከል የተጀመረዉ የድንበር ተሻጋሪ የጭነት ተሸከርካሪዎች ተርሚናል ግንባታ በጥሩ አፈጻጸም ላይ መሆኑ ተገለጸ፡፡
-
የኢፌዴሪ የትራንስፖርት ሚኒስቴር በዚህ ክረምት ለሚከናወነዉ የችግኝ ተከላ መረሃ ግብር የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናቀቁን ገለፀ።
-
የትራንስፖርት ሚኒስቴር ባለሙያዎች የCOVID-19 ወረርሽኝ ስርጭትን ከመግታት አንፃር የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ትራንዚት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የመስክ ጉብኝት አደረጉ፡፡
— 10 Items per Page