የተጀመረው ሀገር አቀፍ የመንገድ ትራፊክ ደህንነት ንቅናቄ ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡
"ከጳጉሜን እስከ ጳጉሜን #እንደርሳለን!" በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀ ሀገር አቀፍ የመንገድ ትራፊክ ደህንነት ንቅናቄ በአዲሱ አመትም ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡
በአዲሱ አመት ዋዜማ የጳጉሜን 5ቱን ቀናቶች በተለያዩ መርሀ-ግብሮች ሲካሄድ የቆየው ሀገር አቀፍ ንቅናቄ በህብረተሰቡ ያላቀ ተሳትፎ ማሳካት ተችሏል፡፡ እንደሚታወቀው የትራንስፖርት ሚኒስቴር #ጳጉሜን_1 የሳይክል እና የእግረኞች ቀን፣ #ጳጉሜን_2 የትራፊክ አደጋን ለመከላከል የእግር ጉዞ እነዲሁም ከብዙሃን ማህበራት ጋር የተዘጋጀ የምክክር መርሃ ግብር፣ #ጳጉሜን_3 የቁጥጥር ቀን ‹‹የቁጥጥር ሥርዓቱን በማዘመን በትራፊክ አደጋ የሚደረሰውን ጉዳት በጋራ እንከላከል።›› #ጳጉሜን_4 “የሚዲያዎች ሚና በመንገድ ደህንነት_ዙሪያ›› እንዲሁም #ጳጉሜን_5 የፍጥነት ገደብን የማክበር ቀን ‹‹መልካም ዜጋ የፍጥነት ወሰንን አያልፍም›› የሚሉ መልእክቶችን መሰረት በማድረግ እየከፋ የመጣውን የመንገድ ትራፊክ አደጋ ለመከላከልና ለመቀነስ የሚያስችል ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ ማከናወን ተችላል፡፡
በንቅናቄው ዘመቻ በአንድ በኩል ሚኒስቴር መስሪያ ቤታችን ባከናወናቸው የፓናል ውይይቶችና ልዩ ልዩ መርሃ-ግብሮች ከህብረተሰቡና ከባለድርሻ አካላት ግብአት መሰብሰብ የቻለበት በሌላ በኩል ለአደጋ መንስዔ ተብለው የተለዩ ምክንያቶችን ህብረተሰቡ ግንዛቤ እንዲጨበጥ እና የመከላከል ስራው ላይ ዋንኛ ተዋናያን እንዲሆን የሚያስችል ወጤት ተገኝቷል፡፡
መንግስት የዜጎችን ደህንነት የማረጋገጥ ሃላፊነትና ግዴታ እንዳለበት ይታመናል በመሆኑም የመንገድ ትራፊክ ደህንነት የአንድ ሰሞን ተግባር ብቻ ሳይሆን ተከታታይና ወጥ ስራ ይጠይቃል ለዚህም "ከጳጉሜ እስከ ጳጉሜ #እንደርሳለን!" ብለን የጀመርነው ሀገር አቀፍ ንቅናቄ በመጪው አዲስ አመትም አጠናክሮ በማስቀጠል ክቡር የሆነውን የሰው ልጅ ከአስከፊው የመንገድ ትራፊክ አደጋ ለመታደግ ከመላው ህዝባችን ጋር በመቀናጀት ለለውጥ እንሰራለን፡፡
"ከጳጉሜን እስከ ጳጉሜን #እንደርሳለን!"
መልካም አዲስ አመት !!
የዜና ክምችት
-
ጥቅምት 1 ቀን 2013 ዓ.ም ከጠዋቱ 12፡00 ጀምሮ የብስክሌት እና የእግረኞች ቀን መርሃ ግብር በየአካባቢው የእግር ጉዞዎች እና የብስክሌት እንቅስቃሴዎችን በማካሄድ የሞተር አልባ ትራንስፖርት የማበረታታት ፕሮግራም ይካሄዳል፡፡
-
‹‹የታዳሽ ሀይል ትራንስፓርት በኢትዮጵያ›› በሚል ርዕስ የምክክር መድረክ ተካሄደ
-
የተጀመረው ሀገር አቀፍ የመንገድ ትራፊክ ደህንነት ንቅናቄ ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡
-
በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር “ከጳጉሜን እስከ ጳጉሜን #እንደርሳለን!” የመንገድ ትራፊክ ደህንነት ንቅናቄ ጳጉሜን 3 #የቁጥጥር ቀን ሆኖ ተከብሮ መዋሉ ተገለፀ።
-
መስማት የተሳናቸው የህብረተሰብ ክፍሎች የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ተጠቃሚ ለማድረግ የአሰራር ማንዋል ተዘጋጀ
-
የትራንስፖርት ሚኒስቴር የአገልግሎት አሰጣጥ ማሻሻያ የአፈጻጸም ሪፖርት ላይ ዉይይት ተደረገ፡፡
-
‹‹የኮቪድ-19 ወረርሽኝና የሎጂስትክስ ዘርፍ›› በሚል ርዕስ 14 ኛው ዙር ዌብናር ተካሄደ
-
በሶማሌ ክልል ደወሌ ላይ የኮቪድ-19 ስርጭትን ለመከላከል የተጀመረዉ የድንበር ተሻጋሪ የጭነት ተሸከርካሪዎች ተርሚናል ግንባታ በጥሩ አፈጻጸም ላይ መሆኑ ተገለጸ፡፡
-
የኢፌዴሪ የትራንስፖርት ሚኒስቴር በዚህ ክረምት ለሚከናወነዉ የችግኝ ተከላ መረሃ ግብር የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናቀቁን ገለፀ።
-
የትራንስፖርት ሚኒስቴር ባለሙያዎች የCOVID-19 ወረርሽኝ ስርጭትን ከመግታት አንፃር የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ትራንዚት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የመስክ ጉብኝት አደረጉ፡፡
— 10 Items per Page