መስማት የተሳናቸው የህብረተሰብ ክፍሎች የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ተጠቃሚ ለማድረግ የአሰራር ማንዋል ተዘጋጀ
ሀገራችን ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግስታትን ድርጅትን የአካል ጉዳተኞችን መብት ኮንቬክሽን ከፈረሙ ሀገራት መካከል ትገኛለች፡፡ ኮንቬክሽኑም አካል ጉዳተኞች ያለአንዳች አድሎ በተለያዩ ዘርፎች ላይ ተጠቃሚዎች ይሆኑ ዘንድ ዋስትና ይሰጣቸዋል፡፡ በሀገራችንም የህግ ማእቀፎችን በማሻሻል መስማት የተሳናቸው ዜጎች ባላቸው እውቀት እና ችሎታ በማንኛውም ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎች ውስጥ ተሳታፊነታቸውን ለማረጋገጥ እየተሰራ ይገኛል፡፡ በዚህ መሰረት የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ አዋጅ 1074/2010 መሰረት በማድረግ መስማት የተሳናቸው ሰዎች አሽከርካሪ ማሰልጠኛ ተቋማት ገብተው የንድፈ ሀሳብና የተግባር ስልጠና በመውሰድ የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ማግኘት እንዲችሉ የአሰራር ማንዋል ተዘጋጅቷል፡፡
በአሁን ሰአት በመሰራት ላይ ያሉ ሰፋፊ የመንገድ አውታሮች ግንባታ፣ የአካል ጉዳተኝነትን ሊያስተካክሉ የሚችሉ የቴክኖሎጂ ውጤት ያካተቱ ተሽከርካሪዎች ለትራንስፖርት አገልግሎት እየዋሉ መሆኑ እና በምልክት ቋንቋ የአሽከርካሪዎችን ስልጠና መስጠት የሚቻል በመሆኑ እንደዚሁም የመንገድ ትራፊክ ቁጥጥሩ ስርዓቱ መስማት ለተሳናቸው አመቺ በመሆኑ መስማት የተሳናቸውን ሰዎች የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ተጠቃሚ ማድረጉ በተሸከርካሪዎች ከቦታ ወደ ቦታ በመንቀሳቀስ የእለት ተእለት ስራዎቻቸውን ማከናወን እንዲችሉ ያደርጋል፡፡
ዋነኛው አላማውም መስማት የተሳናቸው ዜጎች የማሽከርከር መብታቸው ተረጋግጦ የሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ እድገት ቀጣይና ዘላቂ እንዲሆን የራሳቸውን ድርሻ እንዲያበረክቱ ማድረግ እና ማሽከርከር አይችሉም በሚል የተሳሳተ አመለካከትና እና ግንዛቤ የሚፈጥረውን የስራ አጥነት ችግር በመቅረፍ ወደ አምራች ዜጋ መቀየር ነው፡፡
በመሆኑም መስማት የተሳናቸው ሰዎች አሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ ለማግኘት በአዋጅ 1074/2010 መሰረት ለየምድቦቹ የተቀመጠውን ዝቅተኛ የትምህርት ደረጃና የማሽከርከር እድሜ ገደብ በማሟላት ማግኘት ይችላሉ፡፡
የዜና ክምችት
-
ጥቅምት 1 ቀን 2013 ዓ.ም ከጠዋቱ 12፡00 ጀምሮ የብስክሌት እና የእግረኞች ቀን መርሃ ግብር በየአካባቢው የእግር ጉዞዎች እና የብስክሌት እንቅስቃሴዎችን በማካሄድ የሞተር አልባ ትራንስፖርት የማበረታታት ፕሮግራም ይካሄዳል፡፡
-
‹‹የታዳሽ ሀይል ትራንስፓርት በኢትዮጵያ›› በሚል ርዕስ የምክክር መድረክ ተካሄደ
-
የተጀመረው ሀገር አቀፍ የመንገድ ትራፊክ ደህንነት ንቅናቄ ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡
-
በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር “ከጳጉሜን እስከ ጳጉሜን #እንደርሳለን!” የመንገድ ትራፊክ ደህንነት ንቅናቄ ጳጉሜን 3 #የቁጥጥር ቀን ሆኖ ተከብሮ መዋሉ ተገለፀ።
-
መስማት የተሳናቸው የህብረተሰብ ክፍሎች የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ተጠቃሚ ለማድረግ የአሰራር ማንዋል ተዘጋጀ
-
የትራንስፖርት ሚኒስቴር የአገልግሎት አሰጣጥ ማሻሻያ የአፈጻጸም ሪፖርት ላይ ዉይይት ተደረገ፡፡
-
‹‹የኮቪድ-19 ወረርሽኝና የሎጂስትክስ ዘርፍ›› በሚል ርዕስ 14 ኛው ዙር ዌብናር ተካሄደ
-
በሶማሌ ክልል ደወሌ ላይ የኮቪድ-19 ስርጭትን ለመከላከል የተጀመረዉ የድንበር ተሻጋሪ የጭነት ተሸከርካሪዎች ተርሚናል ግንባታ በጥሩ አፈጻጸም ላይ መሆኑ ተገለጸ፡፡
-
የኢፌዴሪ የትራንስፖርት ሚኒስቴር በዚህ ክረምት ለሚከናወነዉ የችግኝ ተከላ መረሃ ግብር የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናቀቁን ገለፀ።
-
የትራንስፖርት ሚኒስቴር ባለሙያዎች የCOVID-19 ወረርሽኝ ስርጭትን ከመግታት አንፃር የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ትራንዚት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የመስክ ጉብኝት አደረጉ፡፡
— 10 Items per Page